Qerro Media Service - QMS's Post

የሽግግር/ጊዜያዊ መንግሥት ማቋቋም፣ ግዴታ እንጂ ምርጫ አይደለም። (It is not an option; it is a responsibility.)

ዛሬ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች ሁሉ ያላቸው አማራጭ፣ ወይ የሽግግር (ጊዜያዊ) መንግሥት ማቋቋምና አገርን ወደ ምርጫ፣ ፖለቲካውንም ወደ ሕገ-መንግሥታዊ ምልክቶች (sign posts) መመለስ፤ ወይም ቁጭ ብለው ሕዝብ በሕገ-ወጥ አምባገነናዊ አገዛዝ ሥር እንዲማቅቅ፣ አገርም ወደ ለየለት ሥርዓተ-አልበኝነት (ምናልባትም ወደ ለየለት የእርስ በርስ ጦርነት) እንድትወርድ መፍቀድ ነው።

ዛሬ ከመዳከም ወይም ከግድ-የለሽነት የተነሳ፣ ሁለተኛውን አማራጭ እንደ አማራጭ ቢወስዱ እንኳን፣ ሄዶ ሄዶ ይሄ የአብይ ቡድን እብደት፣ ወንጀል፣ እና ትርምስ ሲያበቃ፣ ሥራ የሚጀምሩት ይሄንኑ ግዴታ በመወጣት--ማለትም፣ የሽግግር (ጊዜያዊ) መንግሥት በማቋቋም--ነው።

ስለዚህ ይህንን የማይቀርና አማራጭ የሌለውን ታሪካዊ ግዴታ ለመወጣት በመድፈር፣ በአስቸኳይ ጊዜያዊ መንግሥትን መስርቶ አደጋውን መቀነስ ይገባል።

It is not an option; it's a responsibility.

#Abiy_Ahmed_has_expired!
By: via Qerro Media Service - QMS

No comments:

Post a Comment

Featured post

Ethiopia’s controversial quest for the sea

https://ift.tt/4t29xJd Ethiopia is famously landlocked. That’s why the ambitious Ethiopian prime minister Abiy Ahmed has long harbored visi...